Saturday, May 18, 2013

አደገኛ የሕወሓት የሙስና ሰደዶች ከነውርንጭሎቻቸው ሲጋለጡ !!!


አሃዞቹ ምን ያህል የወያኔ ባለስልጣናት 10 መንግስታዊ ድርጅቶችን ተገን በማድረግ በሙስና እንደተዘፈቁ እና ሊዘፈቁ እንዳሰቡ ያመለክታሉ::
እጅ ከፍንጅ ተይዘው በ....ትእዛዝ ተመልሰው ገቢ የሆኑ ወጪዎች... ሆኖም ሙሰኞቹ ስራቸውን ቀጥለዋል::

-የአዲስ አባባ መስተዳድር የመሬት ስራ አመራር ፕሮጀክት ቢሮ በሃሰት ማስረጃ ከመንግስት የእቃ ግዢ መመሪያ በተቃረነ መልኩ ህገወጥ ግዢ ሊፈጸም ሲል ተገኝቶ የ20 ሚሊዮን ብር ፕሮጀችት ተሰርዟል::
-የኢትዮጵያ እህል ንግድ ኢንተርፕራይዝ በህገወጥ መልኩ የቡና መፍጫ ማሽኖች በ5 ሚሊዮን ለመግዛት ሲሞከር ተደርሶበት  ገንዘቡን ተነጥቋል::
-የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን የመሮጫ ካንቫስ በሚል ስም ግልጽ ባልሆነ መንገድ ያወጣው 25 ሚሊዮን ብር ተይዟል::
-ደብረማርቆስ ዩንቨርስቲ በተማሪዎች የምግብ ማሻሻያ ሰበብ ህገወጥ ግዢ ሊፈጽም ሲል ተደርሶበት 291,566 ሺህ ብር ተመላሽ አድርጓል::
-የውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት ባለስልጣን በማይጠበቅ እጅግ ከፍተኛ በሆነ ወጪ በስሩ ለሚገኝ የፕሮጀችት ቢሮ በሚል ስም የመስመር ዝርጋታ እና አቅርቦት በማለት 292 ሚሊዮን ብር በህገወጥ መልኩ ሲያወጣ ተደርሶበት ተመላሽ ሆኗል::
-የግብርና ሚኒስቴር በ36.6 ሚሊዮን ብር ህገወጥ የዘር መፍጫ ማሽን ሊገዛ ሲል ተደርሶበታል::
-ዝቋላ ብረታ ብረት ማቅለጫ ፋብሪካ በ25 ሚሊዮን ኢሮ እጅግ የወደቀ እና ደረጃውን ያልጠበቀ ማሽን የገዛ ሲሆን ይህ ማሽን የስራ ጊዜን እና የሰው ጉልበትን የሚጨርስ መሆኑ የተረጋገጠ ሲሆን ማሽኑም ተችኖ ያልመጣ ሲሆን ይህ ማሽን እንዲቀይእር ተሞክሮ እስካሁን ተመላሽ አልሆነም::ምንም ውጤትም የለም::
-የመሬት አስተዳደር ባለስልጣን/እጅግ አደገኛ የመሬት ሙስኝነት/
ሃሰተኛ እና ህገወጥ ሰነዶችን በማዘጋጀት
1- 3,226 ስ.ሜ. መሬት ..21.1 ሚሊዮን ብር የሚገመት ጉዳዩ በፍርድ ሂድት ላይ ያለ
2- 3,837 ስ.ሜ. መሬት ...25.1 ሚሊዮን ብር የሚገመት ጉዳዩ ለህግ ውሳኔ የተላከ
3- 128,000 ስ.ሜ መሬት ...842 ሚሊዮን ብር የሚገመት ጉዳዩ በምርመራ ላይ ያለ..
-የገቢዎች አስተዳደር
47.9 ሚሊዮን ብር የገቢ ታክስ በማጭበርበር ጉዳዩን በማድበስበስ በመሞከር ሲባል የተያዘ ሰነድ ጉዳዩ ለህግ የቀረበ
10.7 ሚሊዮን ብር ለአፋር መስተዳደር ለማስተላለፍ ታስቦ ገንዘቡ በባለስልጣናት የተሰረቀ ሲሆን ባለስልጣኖቹ በቅርቡ ለመክሰስ ዝግጅቱ ተጠናቋል::
-ወያኔ የዘረፋቸው የህዝብ ሃብቶች
146.6 ሚሊዮን ብር + 2.9 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላርስ  በተለያዩ የግዥ እና ከጨረታ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች በባለስልጣናት ተዘርፏል::
75.3 ሚሊዮን ብር ለፊንጫ ስኳር ፋብሪካን ለማስፋፋት የደን ምንጠራ የሸንኮራ አገዳ መትከያ እና የመኪና መከራያ በሚል ሰበብ ተዘርፏል::
-ሁለት ዳኞች እና ሁለት ጠበቆች የእጅ በእጅ ሙስና ሲፈጽሙ ተይዘው ጉዳያቸው ለህግ ሊቀርብ ነው::
-የተለያዩ ወንጀሎች
10 ሚሊዮን ብር +200,000 የአሜሪካ ዶላር በመንግስት ከፍተጛ ባለስልጣኖች ተዘርፏል::ገንዘቡን በግል እና በቼክ ማጭበርበር ፈጽመውታል::
6.2 ሚሊዮን ብር ከኢትዮያ አየር መንገድ ተጓዦች የተነጠቀ..ምርመራ ላይ ያለ:;
ምንጩ ያልታወቀ 7.4 ሚሊዮን ብር በባለስልጣናት ዘንት የተገኘ...
3.8 ሚሊዮን ብር  በጉቦ የተገኘ ህጉ በተሻረው የፍራንኮ ቫሉታ ስም እቃዎችን በማስገባት በመፍቀድ ...ህገወትጥ ለሆኑ የውጭ ሰዎች የመግቢያ እና የመውጫ ቭዛ በመስጠት የተገኘ የሙስና ገንዘብ

እስካሁን የዚህ የሙስና ተጠቂ የሆኑ ባለስልጣናት እና ተባባሪዎቻቸው የታገደባቸው/የተያዘባቸው ንብረት እና ገንዘብ
128,709.3 ስ.ሜ.መሬቶች.......28 ዘመናዊ የግል መኪኖች....64 ዘመናዊ መኖሪያ ቤቶች ....11 ድርጅቶች....2.8ሚሊዮን ብር .....15.1 ሚሊዮን ዶላር የተያዘ ሲሆን
አራት ህንጻዎች እና , 1,945 ስ.ሜ መሬት እና 21.1 ሚሊዮን ብር ወያኔዎች ከወያኔዎች ወርሰዋል::

Wednesday, May 15, 2013

ወያኔ እያዘናጋን ነው እየተዘናጋ??? ህዝባዊ ጥያቄ መመለስ መፍትሄ ነው!!!

ወያኔ እያዘናጋን ነው እየተዘናጋ???
ምንሊክ ሳልሳዊ
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ህዝባዊ ጥያቄዎች እየበረቱበት የመጣው ወያኔ መላወሻ በማጣቱ የሚያደርገውን እስካለማወቅ ደርሷል:: ከእነዚህም ድንብርብሮች አንዱ ከአባቱ ሻእቢያ እንደወረሰው የፈጠራ ወሬ በአለም አቀፍ ደረጃ ማሰራጨት ነው:: እንዲሁም የህብረተሰቡን ጥያቄዎች ያስረሱልኛል ጭንቅላት ይሰርቃሉ የሚል እደምታ ያለውን ፈጣን ዘገባ ማሰራጨት ስራዬ ብሎ ይዞታል::

ባለፉት 21 አመታት የአገዛዝ ዘመኑ ወያኔ ስልታዊ የሆኑ ያልሰለጠኑ እና ጫካዊ ብልሃቶችን ለመፍጠር እና ሲነቁበትም አለማቀፍ ሽብርን ይፈጥራሉ የሚለውን ወንጀል በዜጎች ላይ በመላከክ የትግል መሪ ሃሳቦችን ወደ አንድ አቅጣጫ ሊነዳቸው ይፈልጋል::የህዝቦችን የመብት እና የነጻነት ጥያቄ መመለስ ያቃተው ወያኔ በሚፈጥራቸው የፈጠራ ወሬዎች ህዝቡን ለማደንዘዝ እና ለማዘናጋት እየዳከረ ይገኛል::
የፊተኞቹን ጥለን የቅርቦችን ስናስባቸው የሙስሊሙን ጥያቄዎች ተከትሎ የክርስቲያኑን አንድነት ያየው ወያኔ ተደናግጦ በባህር ዳር ደራሲ በኣሉ ግርማ በምንኩስና ተገኛ በማለት የህዝቡን አትኩሮት ለማሳብ ያደረገው ሙከራ ህብረተሰቡ ፊቱን ወደ ባህር ዳር አትኩሮ ትግሉን እንዲያዘናጋ ያደረገው ሙከራ የከሸፈበት ሲሆን ይህንን ተከትሎም ከፍተኛ ውግዘት ያስከተለውን በቤንሻንጉል ጉምዝ የተፈናቀሉትን የኣማራ ተወላጆችን ሁኔታ ለመደባበቅ የሻእቢያ እና የወያኔ የእንግሊዝ ወኪሎች እነ ዘርኣይ በምስራቅ አፍሪካ የተነሳባቸውን የአበሻ ትኩሳት ለመፈንገል ይረዳቸው ዘንድ መንግስቱ ሃይለማርያም ሞተ ብለው በቶፒክስ ድህረገጽ እንዲሁም ለእኛ ለሚያውቁን ደሞ በSMS ላኩና ወሬውን እንድያመለስ አድርገን አስፍተን አራገብነው ::ወያኔ ይታወቃት አይታወቃት አላውቅም እንጂ የህዝቡን ጭንቅላት ለመስረቅ የምታደርገው ጥረት እስካሁን አልተሳካላትን ህዝብ ለ 2 እና 3 ቀናት ሊዘናጋ ይችላል እንጂ ለዘላለም አይዘናጋም:: በርግጥ የትግል እረፍት የለውም ለነሱ የስልጣን ማስረዘሚያ ለጫ ደሞ የትግል እረፍት ሊሆን ይችላል::
በዚህ ያላረፉት ወያኔዎች የአባይ ቦንድ በመሸጥ ኪሳቸውን ለማደለብ እና ህገወጥ የኢኮኖሚ አሸባሪነትን በአለም ላይ ለማስፋፋት ፈልገዋል ተብለው በአብዛኛው ዲያስፖራዎች በመወንጀላቸው በየሄዱበት በመዋረዳቸው የሚቀይሱት ነገር ቢያጡ የኢትዮጵያን ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤትን በመወንጀል አትኩሮት ሊያገኙበት ያቀዱትን ነገር ባለማሳካታቸው በተለያ መልኩ ሲመክሩ ውለው እና አድረው ሁኔታዎችን ወደራሳቸው ባለስልጣኖች በማዞር በሙስና ስም ቱባዎችን ወደ እስር ቤት ወረወሩ:: የሚዘናጋ ግን አልነበረም::
ይልቁኑ የራሳቸው ደጋፊዎች እና ተቃዋሚ ዲያስፖራዎች በሃገር ውስጥ ያለው የሰብኣዊ መብት አያያዝ የፖለቲካ እና የሕሊና እስረኞች .....የኑሩ ውድነት የመዘዋወር መብት የሃይማኖት እና የህግ ጉዳይ ጥያቄዎችን አንግበው ተነስተውባታል ወያኔ ላይ:: በምንም ነገር ህዝብን በማዘናጋት ትግልን ለማሰልሰል የተደረጉ ሙከራዎች አይሳኩም ህዝባዊ ጥያቄዎች ሲመለሱ የዛን ጊዜ ...የፖለቲካ እና የህሊና እስረኞች ሲፈቱ ያን ሰአት ...ህዝብ ጠግቦ ሲያድር...መልክም አስተዳደር ሲሰፍን ሰው በእውቀት ሲሰራ ጎሳ መቁጠር ሲቆም ...እና ተመሳሳይ ጥያቄዎች ሲመለሱ ህዝብ አርፎ ይቀመጣል::
የወያኔ ጁንታ በሙስና ስም የራሱን አብዮት በማካሄድ በዲያስፖራው ዘንድ የአንበሳነት ተሰሚነት ለማግኘት ሲል ይህን ሰሞን በቱባ ባለስልታኖቹ ላይ ወረራ የጀመር ሲሆን ይህችን ሰበብ በማድረግ የህዝቡን ጭንቅላት ሰርቆ ለማዘናጋት ያደረገው ሙከራ ስላልተሳካለት ወዲያው ነበር ስብሰባ የተቐመጠው ከውስጥ እና ከውጭ እንዲሁንም ከኣባላቱ የመጣበትን ጫና ያልቻለው ደረቁ ወያኔ ምንም ብልሃት ቢፈጥር ማንም ሊዘናጋ ባለመቻሉ የመጨረሻ እርምጃዎችን ለመውሰድ እያስጠና እንደሆነ ተደርሶበታል::
ህዝብን ያዘናጋ እየመሰለው የተዘናጋው ህዝብን ያፋጀ እየመሰለው ያፋቀረው ወያኔ እንደት እንደሚሳካለት ባለማወቁ እየዳከረ ነው:: ይህን ሰሞን በባህር ዳር የተከሰተውን የጅምላ ግድያ ተከትሎ ደሞ የስርኣቱን ንዝህላልነት እና እየደከመ ለመውደቅ መንገዳገዱን እንዳያሳብቅበት ይመስላል የተለያየ ዘዴ በመፍጠር እና በማስወራት ራሱን ለትዝብት ዳርጓል:: ወያኔ ራሱ ያሰለጠነው የፖሊስ ሰራዊት በፈጠረው የዲሲፕሊን ግድፈት ተራ በሆኑ ጉዳዮች ምን ያህል የወታደሩ እና የፖሊሱ ክፍል ልፍስፍስ መሆኑን ያመለክታል ::ይህ ጉዳይ መከሰቱ በሙስና ላይ የማደርገው ዘመቻ ብሎ የጀመረው እና በሕወሓት የጦር ጄኔራሎች ተቃውሞ የመጣበት ነገር እንደአዘናጋለት እና በዚሁ ሙስና ያለው ዘመቻ ተድበስብሶ በባህር ዳር ወንጀል ሽፋን እንደቀረለት የተረዳው ወያኔ ምን እና እንዴት ወደ ህዝብ እንደሚዘልቅ ጨንቆታል::ከዚህ ጋር አያይዞ ህዝብን በዘር ለማጋቸት ገዳይ እንዲህ ነው ሟቾች እንዲህ ናቸው በማለት የብሄር ፖለቲካ በማራገብ ህዝብ ወደ ትግል ፊቱን እንዳያዞር እና እርስ በእርሱ እንዲባላ የወጠነው ሴራም ከሽፎበታል::ወያኔ ተዘናጋ::
በሜይ 25 2013 በ አፍሪካ ህብረት ደጃፍ ሊካሄድ የታቀደው ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ አስደንግጦት መላ እየፈለገ የሚገኘው ወያኔ ካድሬዎቹ ሁላ ነጭ ልብስ ለብሰው ከተማውን እንዲዞሩ በጀት መመደቡ ደሞ ይህን ሰሞን ያደረገው የመዘናጋት በሽታው ነው ህዝብን አዘናጋለሁ ብሎ ራሱ በመዘናጋት በሽታ የተጠቃው ወያኔ ለህዝባዊ ጥያቄዎች መልስ ቢሰጥ የተሻለ ይሆናል:: የዛኔ ህዝብን ማዘናጋት ይቻላል :: ህዝባዊ ጥያቄዎች ታዝለው ግን ረዥም ማንገድ መሄድ አደጋ ስላለው የተዘናጋው ወያኔ በፌዴራል ዱላ ሽባ እናደርግሃለን የሚለው ህዝብ ባባዶ እጆ ወያኔን ሽባ እያደረገው ነው::
ወያነ አዘናጋለሁ ብሎ የተዘናጋ የአሸባሪዎች ስብስብ መሆኑን በቅርቡ ይመለከቱታል::ይጠብቁ::
ህዝባዊ ጥያቄ መመለስ መፍትሄ ነው::

Saturday, May 11, 2013

"ባንድ ወንጭፍ አማራውን በፍጥነት!!!"ሕወሓት ብኣዴንን እየዋጠው ነው!!

ከዚህ መሃል  ቁጥር 2 አቶ ገብረዋህድ ትግሬ ናቸው 
ሕወሓት ብኣዴንን እየዋጠው ነው!!
"ባንድ ወንጭፍ አማራውን በፍጥነት!!!"

ከበረሃው ትግል ጀምረው አብረው እየነጎዱ የመጡት ሕወሓት እና ኢህዴን በኋላም ብኣዴን በአሁኑ ወቅት አጅግ ከባድ የሆነ የፖለቲካ ፊቲጫ ውስጥ መሆናቸውን በዙሪያቸው የሚደረጉት ድርጊቶች እያሳበቁ ነው::በሽግግር መንግስቱ ጊዜ ታምራት ላይኔ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኖ በነበረበት ወቅት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ዙሪያ የቀድሞ የኢህኣፓ ሴሎች መሰባሰብን ተከትሎ እንዲሁን ጣምራት የነበረው አቋም ተለክቶ በኤርትራ ጉዳይ ዙሪያ ያለው አመለካከት ተመዝኖ በወያኔ እና በሻእቢያ ጥርስ ውስጥ ገብቶ በሙስና ተፈርጆ በከባዱ አንገቱ እስኪሰብር ቀጥቅውት ከፖለቲካ ጨዋት ውጭ አድርገውታል::
እንዲሁም የአዲስ አበባ ከንቲባ የነበረውን ሙሉአለምን በፈንጂ ባህር ዳር ላይ አጥፍተውታል:: የሕወሓት የፖለቲካ ቁማር በዚሁ አላበቃም መለስ ብለን ካየነው ብዙ ነው.....እያለ የቀጠለው የሕወሓት መጦ መትፋት እነ አዲስ ለገሰን እነ ተፈራ ዋልዋን እና ሌሎች የብኣዲን አባላትን ከህዝብ ጋር ከተቀላቀሉ በሁዋላ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ሸተዋል በሚል መርዛዊ ጥላቻ በጡረታ በጤና ሰንክ በአምባሳደርነት ከአጠገቡ አባሯቸዋል::ለሃገራቸው ይሰራሉ ተብለው የተገመቱ የተጠበቁ የብኣዴን ታጋዮችን ወዴት እንደደረሱ እንኳን ሳይታወቅ አንጠባጥቧቸዋል:: በተጨማሪም በወታደሩ ክፍል የነበሩትን የብኣዴን ጀነራሎች እና የበታች መኮንኖች ለስልጣን ያሰጋሉ በሚል በተለያዩ እስር ቤቶች በመፈንቅለ መንግስት ሙከራ እና በፖለቲካ ስም አስሮ ይገኛል::በቱረታም አባሯል::
ይህን ይህን ያን ያን  ...እያልን ያለንበት ላይ ስንደርስ ደሞ ከመለስ ዜናዊ ሞት በኋላ በስልጣን ሽኩቻ ዙሪያ የተለያዩ መፋጠጦች እንደነበሩ እንዲሁም እንዳሉ ይታወቃል::ያ መፋጠጥ እና መሿኮት ቀጥሎ በኢህኣዴግ ስብሰባ ላይ በጡዘት ወቶ የነበረ ቢሆንም አልስፈላጊ አደርባይ ሙሰኛ በሚል አደገኛ እንደ ጌታቸው ሴኩትሬ አባባል "የገማ ቂቤ" እየተቀቡ አፋቸውን እንዲይዙ ተደርጓል ብኣዴኖች::
ሕወሓት ለያዘው አላማ እንቅፋት እንደሚሆንበት ከጅምሩ በብኣዴን ላይ የሾሉ ጥርሶቹን እየደጋገመ ሲሞርድ እንደነበር ይታወቃል:; ብኣዴኖች በተለያየ ጊዜያት በሙስና እንዲዘፈቁ እና ማስረጃ እንዲያዝባቸው በአጠገባቸው በሚመደቡ የህወሓት አባላት ከፍተኛ የሆነ ውስወሳ እና ክትትል በማድረግ መዝገባቸውን በሙስና ሰነዶች በመሙላት ለማስወገድ ሚናውን ተጫውቷል:: አሁንም እየተጫወተ ነው:: እንዲሁም ይህንን የፖለቲካ ቁማር በደቡብ ግንባር ላይም እየተጫወተ ይገኛል::
ሕወሓት ነባር የብኣዴን ታጋዮችን ሰብሰቦ ካስወገደ በኋላ በአማራው ክልል የተወለዱ አማርኛ ተናጋሪ ኤርትራውያንን እና የትግራይ ተወላጆችን በመሰግሰግ ጉዞውን ሊቀጥል እየተራወጠ ይገኛል::

ህወሓት በዚህ ሰሞን ደሞ በብኣዴን ባለስልጣናት ላይ ዘመቻ ከፍቷል:: ዘመቻው ሁለት አላማዎችን የያእ ነው እንጂ በፍጹም ሙስና አይደለም::በእርግጥ ሙስና የለም ብለን አንናገርም ሆኖም ሊበሏት ያሰቧትን... እንደሚባለው በፖልርቲካው ላይ ችግር እየፈጠሩ ያሉትን ባለስልጣናት ማስወገድ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ሙስናን እንደቀዳሚ ተደርጎ ለህዝብ ማስነገር አስፈላጊ ነው ...ለመሆኑ በሙስና ረገድ ከፍተኛውን የሙስና ባላባቶች የሆኑ የሕወሓት ባለስልጣናት እና የጦር ጄኔራሎች ለምን አይከሰሱም ? አይባረሩም? አይጠየቁም??...ባለፈው ጊዜያት ከጸረ ሙስና ኮሚሽን ዘሎ የወጣ መረጃ እንደጠቆመው የህወሓት አባላት በሙስና መዘፈቃቸውን የሚያሳይ እውነተኛ ምስክር ነው::
ሕወሓት ውስጥ ተንሰራፍቶ የሚገኘው የሙስና ድርጊት እንደት ነው ሊወገድ የሚችለው?? ለምንስ የህወሃት ሙሰኞች ለፍርድ አይቀርቡም ስልጣናቸውንስ አይነጠቁም?? የጦር ጄኔራል የሆኑ የሕወሓት ቅምጥ መኮንኖችስ ለስልታን ጥበቃ በሚል ሰበብ ለምን ዝም ይባላሉ?? ይህን እና ተመሳሳይነት ያላቸው ጥያቄዎች ለመመለስ የሚከብድ ነው ለወያኔ::
በዚህ ሳምንት ደሞ እንደፋሽን የተያዘው ነገር ቢኖር ብኣዴኖችን መግቢያና መውጫ አሳጥቶ አፋቸውን በማስያዝ ምንም አይነት ጥያቄ እንዳይጠይቁ እና አንገታቸውን እንዲሰብሩ ማድረግ ነው::
ትላንት እና ጠዋት የደረሱን ማስረጃዎች እንዳመለከቱን ከሆነ መገናኛ አከባቢ በሚገኘው የጉምሩክ ዋና መስሪያቤት ውስጥ ሲቭል በለበሱ ደህንነቶች እና በፌዴራል ፖሊስ የታጀበ ኦፕሬሽን እየተደረገ እንደሆነ ቢያመለክትም በውስጥ የነበሩ ከ200 በላይ ሰራተኛች የሃገር ጉዳይ ነው ተብለው እንደወጡ እና አቶ መላኩ ብጫውን ታግቶ እንደነበር እና በኋላም በምን እንደሆነ ሳይታወቅ አቶ ገብረዋህድ እና ሌሎች የመምሪያ ሃላፊዎች በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ተነግሮ ነበር :; ይህንን ለማጣራት በተደረገ ሙከራ መረጃ የሚሰጡን የብኣዴን እና አንዳንድ የሕወሓት አባላት ስልካቸውን እስከ ማታ ድረስ እንዲዘጉ ታዘው ነበር::
መረጃዎች እንደጠቆሙት በአቶ መላኩ ፈንታ እና በአቶ ገብረዋህድ መካከል ምንም አይነት መግባባት እንደሌለ እና በኣንድነት ሙስና ይፈጽማሉ ሊያስብል የሚችል አንድም ሁኔታ የለም ይላሉ እንደውስጥ አዋቂዎች እምነት:: ገብረዋህድ በጉምሩክ ባለስልጣን ውስጥ ፈላጭ ቆራጭ ሲሆን አቶ መላኩ እንደበላይነታቸው ሙሉ ስልጥኣን አልነበራቸውም:: አቶ መላኩ የፈረሙትን ገብረዋህድ ይሽር እንደነበር እና ይህም ጉዳይ ጥቆማ እስከ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደርሶ ውሳኔ ደፍሮ የሰጠ አልነበረም::ገብረዋህድ ማለት እጅግ ቀንደኛ ዘረኛ የሆነ ሰው እንደሆነ ይታወቃል ስለዚህ ኢትዮጵያ ከሚለው መላኩ ጋር ተስማምቶ ሙስና ይሰራል ማለት ዘበት ነው::ታማኝነትም የለውም ::ገብረዋህድ ባንድ ወቅት በመስሪያ ቤቱ እነና ስርኣቱ ህልውናችን አንድ ነው ያለ ደፋር እና ዘረኛ ሰው ነው በሙስና ተብሎ ዘብጥያ መውረዱ አጠያያቂ ሲሆን እንደኔ ብኣዴኖችን ለመጥለፍ የተሸረበ ሴራ ነው::
ገብረዋህድ ከወይዘሮ አዘብ ጋር ቀረቤታ እንዳለው ይታማል:: ከላይ እስከ ታች በጉምሩክ ውስጥ የሞሉት የትግራይ ተወላጆች በሙስና ተጨማልቀዋል::እንዲሁም ስርኣቱ እጅግ ከሚንከባከባቸው ሰዎች አንዱ ነው:: በተለያየ ጊዜ የህወሃት ባለስልጣናት እና የጦር ጄኔራሎች በተለያየ ጊዜ ከውጪ የሚያስገቧቸውን ማንኛውም ነገሮች ጉምሩክ በነጻ እንደሚያሳልፍላቸው ሲታወቅ የህ ደሞ የገብረዋህድ ተትእዛዝ እንደነበር መረጃዎች ይጠቁማሉ::
በመከላከያ ሚኒስቴር ውስጥ ጸሃፊ ሆና የምትሰራ አንዲት የመሃል አገር ሰው የሆነች ትግሪኛ ተናጋሪ እንደነገረችኝ በተለያየ ጊዜያት ከጄኔራሎቹ አልፎ እሷ ራሷ ከተለያዩ አገሮች የምታስገባቸው እቃዎች በነጻነት ቤቷ ድረስ ተጭነው እንደሚመጡ አጫውታኛለች::
ይህን ተከቶ አቶ ብርሃነ ሃይሉ እና አቶ ሴኩቱሬ ጌታቸው በአማራነት ከህወሃት ተባረዋል :: ህወሓት ወዴት እያመራች ነው?? አማራውን እያደነዘዘች ማጥፋት :: ይህ ሊታገሉት የሚገባ ጉዳይ ነው:: ምክንያቱም ባለፉት ጊዜያት የተደረጉ ጉዞዎች ያልጣሟቸው ባለስስልታናት ጥያቄ እያቀረቡ ባሉበት በዚህ ወቅት እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች መመልከት እና ማመዛዘን የራሳችን ድርሻ ነው::

Monday, May 6, 2013

ህገመንግስቱን ማክበር ከገዢው ፓርቲ ይጀመር!!!


ህገመንግስቱን ማክበር ከገዢው ፓርቲ ይጀመር!!!
ምንሊክ ሳልሳዊ
ዞን 9 ኢ-መደበኛ የአራማጆች እና የጦማሪያን ቡድን ኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው ማኅበረሰባዊ እና ፖለቲካዊ ሁኔታ የተለየ እና ወገናዊ ያልሆነ ታረክ ለመፍጠር እየሠራ የሚገኝ የወጣቶች ኢትዮጵያውያን በ2005 ዓ.ም ሊደረጉ ከታቀዱት አራት የበይነመረብ ዘመቻዎች ሦስተኛው የፊታችን ረቡዕ ሚያዝያ 30 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ እስከ አርብ ግንቦት 2 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ ያካሂዳል::
ሶስተኛው የበይነ መረብ ዘመቻ "ዲሞክራሲን በተግባር እናውል፤ የሰላማዊ ሰልፍ መብታችን ይመለስ!" በሚል መሪ ቃል ይካሐዳል:: ሦስተኛው ዘመቻ መንግሥትን እና ሁላችንንም በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 30 የሰፈረውን ‹ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በመሆን መሳሪያ ሳይዝ በሰላም የመሰብሰብ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነጻነትና፣ አቤቱታ የማቅረብ መብት እንድናከብር› የሚጠይቅ ነው፡፡
*********************************************************************
 በዚህ ጉዳይ ላይ የራሴን አጠር ያለ አስተያየት ማስቀመጥ ስላለብኝ ይህንን ለማለት እወዳለሁ::
በሃገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ የዲሞክራሲ ጮራ እንዲፈነጥቅ በተለያዩ ጊዜያት የተነሱ ኢትዮጵያያን ላለፉት 21 አመታት የትግል አስታውጾ አድርገዋል:: እንዲሁም የኢሕኣዴግ ሰራዊት የተሰዋለት አላማም ይህንን የህዝቦች ነጻነት እና እኩልነት ለማረጋገጥ ነበር::በህዝቦች የትግል ሂደት እና መስእዋትነት ተረቆ ጸድቋል የተባልነው ህገመንግስት ግን ከዚህ በተለየ መልኩ የወረቀት ላይ ጀብደኛ ሲሆን በማንም መመሪያ እና የስልክ ቴዛዝ ሲሻር እየተመለከት ነው::
ህገመንግስቱ በወረቀት ላይ ብቻ ህይወት ሳይዘራበት በተድፈነፈነ መልኩ አስፈጻሚ አቶ በግለሰቦች ያውም የህግን ምንነት ባልተማሩ እንደፈቀደ እየተተረጎመ የዜጎችን ህልውና ከመፈታተን አልፎ ማንነትን እስከማሳጣት ድረስ ዘልቋል:: ህገመንግስት የማፈኛ መሳሪያ እንዲሁም የማሰሪያ የመወርወሪያ የመግደያ መሳሪያ ከመሆን አልፎ ጥልቅ አምባገነንነት እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል:: ይህ ማለት ህገመንግስቱ በተግባር አለመተርጎሙ ይህንን ፈጥሯል ማለት ነው::
ማንኛውም በሃገሬ ጉዳይ ያገባኛል የሚል ዜጋ በህገመንግስት መናድ እና መጣስ ጉዳይ እየተከሰሰ ወደዘብጥያ ማውረድ የተለመድ የየእለት ተግባር ሆኗል:;ከ1997/2005 ምርጫ በኋላ ደሞ የባሰ በረቀቀ መንገድ አዲስ ህግ ወቶለት አሸባሪ በሚል ዉንጀላ ህገ መንግስቱ እስከመረሳት ደርሷል::
የሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ዲሞክራሲያዊ መብቶች ሃገራችን ከተቀበለችው አለማቀፍ ድንጋጌዎች አንዱ ነው::ይህ ማለት ደሞ ሰዎች በማንኛውም ጊዜ የሚደግፉትንም ሆነ የሚቃወሙትን ጉዳይ በአደባብይ ወተው ድምጻቸውን ማሰማት ይችላሉ ማለት ነው :: ተረጋግጧል በተባለው  በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 30 የሰፈረውን ‹ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በመሆን መሳሪያ ሳይዝ በሰላም የመሰብሰብ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነጻነትና፣ አቤቱታ የማቅረብ መብት እንድናከብር› በሚል ሰፍሮ ይገኛል::
ይህ አንቀጽ 30 ግን እንደ በላይ ህግ ሳይተይ ከ1997/2005 ጀምሮ በበታች ህጎች ተገድቦ ይገኛል:: የበላይ ህጎች የበታቾቹን በሚገድቡበት እንጅ የበታቾች የበላያቸውን በሚሸረሽሩበት ሂደት ዉስጥ አልም አልፋበት ባለማወቋ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ዜጎቿን እያጣችበት እየተገፈፈችበት ነው::
የገዢው ፓርቲ እሱን ብቻ የሚደግፉ ሰላማዊ ሰልፎችን እንዲደረጉ ከመፍቀድ ዉጪ የተቃውሞ ሰልፎችን በማኮላሸት ተቃዋሚዎችን ወደ እስር ቤት ያግዛል:: አሁን እንኳን በቅርቡ አለማቀፍ ማህበረሰብ የሚያወግዘው የፋሺስቱ ግራዚያኒን ሃውልት ግንባታ ለመቃወም የወጡ ዜጎች በጋራ ሃገራዊ ጉዳይ አብሮ መስራት የሚገባው ገዢው ፓርቲ ፖሊሶችን በማሰማራት አፍሶ ወደ እስር ቤት ወስዶ ካሰራቸው በሗላ ፈቷቸዋል :;ይህ የሚያሳየው እንግዲህ ምንን እንደሆነ እርሶው ይደምድሙት::
ስለዚህ  ይህንን የሰው ልጆች የማይገሰስ ህገመንግስታዊ መብት ገዢው ፓርቲ ማክበር ከራሱ እንዲጀምር እናሳስባለን::አመሰግናለሁ::ምንሊክ ሳልሳዊ
***************************************************************
ከዚህ በታች የምታነቡት የዞን 9 ሦስተኛው የበይነ መረብ ዘመቻ ጋዜጣዊ መግለጫ ነው::ዲሞክራሲን በተግባር እናውል፤ የሰላማዊ ሰልፍ መብታችን ይመለስ!
ሦስተኛው የበይነ መረብ ዘመቻ ጋዜጣዊ መግለጫ

ዞን 9 ኢ-መደበኛ የአራማጆች እና የጦማሪያን ቡድን ኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው ማኅበረሰባዊ እና ፖለቲካዊ ሁኔታ የተለየ እና ወገናዊ ያልሆነ ታረክ ለመፍጠር እየሠራ የሚገኝ የወጣቶች ኢትዮጵያውያን ነው፡፡ ይህንን የምናደርግበት ዋና ዓላማ ሁሉም ኢትዮጵያውያን የሀገሪቷ ጉዳይ ያገባኛል ብለው ውይይት የማድረግ ባሕል እንዲያሳድጉ በማድረግ ሀገሪቷን በሁሉም መስኮች ወደተሻለ ደረጃ የሚያደርሱ ሐሳቦች እንዲወለዱ ለማመቻቸት ነው፡፡

የተከበራችሁ የዞን9 ነዋሪዎች፣ በ2005 ዓ.ም ሊደረጉ ከታቀዱት አራት የበይነመረብ ዘመቻዎች ሦስተኛው የፊታችን ረቡዕ ሚያዝያ 30 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ እስከ አርብ ግንቦት 2 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ ይካሄዳል፡፡ ሦስተኛው ዘመቻ መንግሥትን እና ሁላችንንም በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 30 የሰፈረውን ‹ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በመሆን መሳሪያ ሳይዝ በሰላም የመሰብሰብ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነጻነትና፣ አቤቱታ የማቅረብ መብት እንድናከብር› የሚጠይቅ ነው፡፡

ሰላማዊ ሰልፍ እና ስብሰባ የማድረግ መብት ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌ የተደረገለት ዜጎች ድጋፋቸውን ወይንም ተቃውሟቸውን ከመሰሎቻቸው ጋር በመሆን ሐሳባቸውን መግለጽ እንዲችሉ እና ያገባናል የሚሉት ጉዳይ ላይ ሐሳብ እዲለዋወጡ እና እንዲወያዩ ነው፡፡

የ1997 ዓ.ም ምርጫ ቅስቀሳ አካል የነበሩት የሚያዝያ 29 እና 30 ሰልፎች በኋላ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ እና መሰብሰብ መብት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለተወሰነ ጊዜ ተገድቦ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ከዛ በኋላ የተካሄዱ ጥቂት ሰላማዊ ሰልፎች የአንድ ወገን ሐሳብ የሚንጸባረቅባቸው እና ለዚያም ሲባል ይሁኝታን ያገኙ ብቻ ነበሩ ማለት ይቻላል፡፡ ከሚያዝያ 30፣ 1997 ወዲህ ተቃውሞን አስመልክቶ የተደረገው ሰልፍ የወ/ት ብርቱካንን መታሰር አስመልክቶ የተካሄደ ሲሆን 250 ሰዎችን ብቻ ያሳተፈ ነበር፡፡ በወቅቱ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች በሰልፉ ላይ ለሚኖረው የደህንነት ችግር ኃላፊነት እንዲወስዱ መጠየቃቸው የተሳታፊዎችን ቁጥር ለመቀነስ መገደዳቸው ይታወሳል፡፡

ፖለቲካዊ በሆኑ ጉዳች ዙሪያ የሚደረጉ ስብሰባዎችም ቢሆኑ በግልጽ ተአቅቦ ባይደረግባቸውም የተለያዩ አስተዳደራዊ ጫናዎችን በመፍጠር እንዳይካሄዱ የእጅ አዙር ክልከላ ይደረግባቸዋል፡፡ ከመንግሥት የእጅ አዙር ክልከላ ሲያልፍም የመሰብሰቢያ ቦታ አቅራቢዎች ከሚደርስባቸው ቅድመ ማስፈራራርያ ወይንም ይደርስብኛል ብለው ከሚያስቡት አስተዳደራዊ በደል የተነሳ መሰብሰቢያ አዳራሾችን ይከለክላሉ፡፡
የሦስተኛው ዘመቻ ዓላማ መሣሪያ ሳይዙ ሰላማዊ ሰልፍ እና ስብሰባ የማድረግ ሕገ መንግሥታዊ መብታችን ላይ የተጣሉ ቀጥተኛ እና የእጅ አዙር ገደቦች እንዲነሱ መጠየቅ ነው፡፡

ዘመቻው በዋነኛነት የሚካሄደው ‹‹ፌስቡክ›› እና ‹‹ትዊተርን›› (#Assembly4Every1 እና #Demonstration4Every1 የሚሉ ኃይለቃሎችን) በመጠቀም ይሆናል፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ እና ስብሰባ የማድረግ ሕገ መንግሥታዊ መብታችንን በተመለከተ የተለያዩ ጽሑፎች በጦማራችን የሚወጡ ሲሆን በፌስቡክ እና በትዊተርም ላይም ይለቀቃሉ፡፡ በሁለቱ (የዞን9 እና የሕገ-መንግሥቱ ይከበር!) የማኅበረሰብ ገጾች ላይ ለዚሁ ዘመቻ ሲባል የተዘጋጁ አጫጭር ጽሑፎች ይሰራጫሉ፡፡ ዘመቻውን የሚመለከት ‹ባነር› ተዘጋጅቶ ዘመቻው በሚቆይባቸው ቀናት የተለያዩ ፕሮፋይል ምስሎችም ተዘጋጅተው የሽፋን ምስል እና የፕሮፋይል ፎቶ ይሆናሉ፡፡

በዚሁ አጋጣሚ ለመላው የዞን9 ነዋሪዎች እና በሰላም የመሰብሰብ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነጻነትና፣ አቤቱታ የማቅረብ መብት ተከብሮ ማየት ለምትፈልጉ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ ጉዳዩ ላይ ያላችሁን አመለካከት፣ መብቱ የተጣሰባቸውን ክስተቶች በማካፈል በጉዳዩ ላይ በመወያየት እንዲሁም የፕሮፋይል ፎቷችሁን በመቀየር በዞን9 ጦማር እና በ‹ዞን9› እና ‹ሕገ-መንግሥቱ ይከበር› የፌስቡክ ገጾች የዘመቻው ንቁ ተሳታፊ እንድትሆኑ በትህትና እንጋብዛለን፡፡

ስለሚያገባን እንጦምራለን!!!
ዞን9



Friday, May 3, 2013

የወያኔ ሰው በላ ምድር ቤቶች በአዲስ አበባ ክፍል ሁለት

የምድር ቤቱ ገበና ...አብዛኛው ከጨለማ ክፍሉ ተንቷል የተወሰኑ ሰዎች በትንሿ መስኮት በኩል ግማሽ ፊታቸው ይታያል በኮሪደር እንጅ ለነሱ መብራት የለውም ...አንድ ድምጽ ሰማሁ  ወርኪቾ ነኝ ገደባኖ የሚል ያዝኩት የተናገረውን ...ፊታቸው ቢጫ የሆኑ ሰዎች በአንድነት ለችንት ቤት በሚል ከለሊቱ 9.30 ላይ ወተው እዛው ምድር ቤት ካለ መጸዳጃ ቤት አተርታ ይዘውል 14 መጸዳጃዎች አሉ ...ቆጠርኩ ላያቸው ስጠጋ መለሱኝ ..ያንተ ጉዳይ ገና ነው አለኝ አንዱ መቀላቀልሽ አይቀርም አትቸኩይ ...ነብሲ አለኝ ሌላኛው.....ይቆይ የተባልኩበት ክፍል ሆኔ እንዳለሁ 10.32 ደቂቃ ሲል ተጠራሁ...እስከዛ ጊዜ ድረስ አልፈተሹኝም ....ምንም የመታኝ የተናገረኝ ሰው አልነበረም  .....ሰው ይፈልግሃል ተባልኩ ፊጠ ተሸፈነ  መኪና ላይ ጫኑኝ  ወሰዱኝ..ራሴን ያገኘሁት አዲሱ ገበያ ተብሎ ከሚጠራው አከባቢ ማንጊያው ላይ ነበር...ይቀጥላል....
የወያኔ ሰው በላ ምድር ቤቶች በአዲስ አበባ ክፍል ሁለት
ባለፈው እንዳነበብነው በምድር ቤት ባለው የወያኔ እስር ቤት ያሉ ከተለያዩ ቦታዎች እንዲሁም ከጎረቤት አገራት የታፈኑ እና በወታደሩ ውስጥ ችግር ይፈጥራሉ ተብለው የታሰሩ ሰዎች ሲሆኑ እነዚህ ቤተሰቦቻቸው የት እንዳሉ እንኳን የማያውቁ ታፋኞች በየምድር እስር ቤት ውስጥ ስንቱ እንዳለ ቤት ይቁጠረው ::
በደረስኩበት የምድር እስር ቤት ውስጥ በትግሪኛ ቋንቋ የሚያወሩ ኡዚ የታጠቁት የድህንነት አባላት ፊታቸውን አፍፈው ነው የሚመለከቱት .. ኡቃቤ አምላካቸው ማንንም አይወድም መሰል ወይም እንዴት እንደሰለጠኑ ባይታወቀኝም ለሰዎች ያላቸው አመለካከት ግን ፊታቸው ላይ ይነበባል::አንተ አንቺ....ሁላችን እነሱ ፊት ርካሽ ትንኞች ነን::እጅግ ጨካኝ መሆናቸውን ከግንባራቸው ታውቃለህ :; ርህራሄ የለሾች ካለፍርድ አስፈላጊ በሆነ ሰአት ሰው በመግደል የደም ጥማቸውን የሚወጡ መሆናቸው ያስታውቃሉ:: በምድር ቤቱ በ5 ሜትር ርቀት የሚገኙት እነዚህ ባለኡዚዎች የደንብ ልብስ ሳይሆን የራሳቸውን ነው የለበሱት:: የደንብ ልብስ የላቸውም::ምድር ቤት ቀዝቃዛ በመሆኑ አብዛኛዎቹ ወፈር ያሉ ልብሶችንን እና የቆዳ ጃኬቶችን ለብሰዋል::አስተያየታቸው ለማያውቃቸው ያስፈራል::......ከነሱ ጋር ከተግባባህ ግን እጅግ መልካም ነገሮችን ታገኛለህ ::አንዱን ወዳጅ ካደረከው ከሚቀርብልህ በላይ በድጋሚ ይቀርብልሃል:: ምግብ ሲጋር ዉሃ ....ግርፋት የቀኑ ከ 5 ወደ 3 ይወርድልሃል:: ወገኖቻችን እየተሰቃዩ በሚገኝበት የምድር ቤት እስር በቶች አንዱን ማየቴ ገመናቸውን አደባባይ እንዲወጣ እግዛቤር እንዳዘዘባቸው እንኳን ሊቆጥሩት አልቻሉም :: እንደዚህ አይነት ስንት እስር ቤቶች እንዳሉ እስኪ ራስዎን ይጠይቁ:: በለስላሳ ብዙ በማያሳዩ መብራቶች ቲኒሽ ኮሽታ በሚሰማበት ጸጥረጭ ባለው የምድር ለምድር እስር ቤት ውስጥ ስንቱ ተገረፈ ተገደለ እዛውስ በሰበሰ??/ያልተመለሰ ጥያቄ ነው::
ለሰአታት በቆየሁበት የሕወሓት ከፍተኛ ሰዎች ብቻ በምስጢር ይቅኦጣጠሩታል በተባለው በዚህ የምድር እስር ቤት ውስጥ ከ60 ሰዎች በላይ ታስረዋል :: ካስፈቱኝ አካላት ለማረጋገጥ እንደቻልኩት ከነዚ ሰዎች 30ፐርሰንቱ የቀድሞ የደርግ መኮንነች የነበሩ እና ከወያኔ የጫካ ትግል ጋር ተቀላቅለው የነበሩ ሲሆን አካሄዳቸው እጅግ የሚያሰጋ እና በወታደራዊ ሳይንስ በምስራቅ አውሮፓ የሰለጠኑ ናቸው...ቀሪዎቹ ደሞ ታጋዮች የነበሩ ሲሆኑ ከባድ የሆነ የሕወሃት ሚስጥሮች በጃቸው ያለ ቢለቀቁ ሕወሓትን ለመጨረሻ ጊዜ መሞቱን የሚያበስሩለት ናቸው ተብለው የተፈሩ ሲሆን እንዲሁም ፓርቲው አዲስ አበባ ውስጥ በሰራቸው ወንጀሎች የተሳተፉ ሰዎችም.... በዚሁ ምድር ቤት ውስጥ ታስረው ይገኛሉ::
በአንድ የስራ ወቅት ያየሁት በሰሜን ሸዋ መውጫ መንገድ ያለው የአለባቸው ጫካ እንዲሁ በደን የተከበበ ሲሆን አሁን ወያኔ ወደ መቀሌ አዘዋውሮቸዋል ተብሎ የሚገመቱት የቀድሞ የኢሕኣፓ አባላት እና ኢትዮጵያውያን ምሁራን ታፍነው ተወስደው የታሰሩበት ቦታ ነበር በአሁን ሰኣት የተወሰኑ የቀድሞ ታጋዮች እና ሻእቢያ በአደራ ያስቀመጠቻቸው ታሳሪዎች ይገኛሉ::
በአዲስ አበባ ታስረው በምድር እስር ቤት ውስጥ የሚገኙ ሰዎች የስርኣት ለውጥ ሳይሆን የሚሹት አዲስ ኢትዮጵያን እና አዲስ ህሳቤን ነው ምክንያቱን ከቀድሞው የስርኣት ለውጥ እንዳየነው ወያኔ ደርግን ሲደመስስ በተለያዩ አከባቢዎች ያገኛቸውን ታሳሪዎች የፈታቸው የተወሰኑትን ሲሆን ሌሎችን እዛው አስሮ አስቀርቷቸዋል::እስካሁንም ያሉ አሉ የሞቱም በምስጢር ተቀብረዋል:: በተለያዩ ዘመናዊ የማሰቃያ ማሽኖች የተደራጁት እነዚህ የምድር ቤት የወያኔ እስር ቤቶች በብዛት የሚገኙት ከአሮገው አይሮፕላን ማረፊያ ጀርባ እና ከብስራተ ገብሬል አከባቢ መሆኑን ውስጥ አዋቂው ሲጠቁሙኝ እንዲሁም በፈረንሳይ ሌጋሲዮን በቦሌቡልቡላ በገርጂ  በካራ በአያት መንደር ውስጥ በገፈርሳ አከባቢዎች በተንጣለሉ ቭኢላዎች ስር በተገነቡ ምድር ቤቶች እየተሰቃየ ያለውን ቤቱ ይቁጠረው::ለሊቱን በአፈና ስራ ላይ የሚሰማሩት ሃይሎቻቸው እንዲሁ አስፈላጊም ከሆን ቀን ለቀን ከፌዴራል ፖሊሶች ጋር በጋራ እንደሚሰማሩ ታውቋል:: ስራቸው ማፈን ብቻ ሳይሆን መግደልም እንደሆነ የተነገረላቸው የጁንታው ጃይንቶች በአዲስ አበባ መኖሪያቤት የላቸውም:; አብዛኛዎቹ የመጡት ከትግራይ እና ከኤርትራ ሲሆን አስፈላጊው ነገር ሁሉ እንደሚሟላላቸው እና ለቤተሰባቸውም እንዲሁ ሁሉም ነገር እንደሚደረግ ሲረጋገጥ ምንም አይነት ምስጢር እንዳያወጡ ከፍተኛ ክትትል አንዱ ባንዱ ላይ ያደርጋል ትንሽ ፍንጭ የተገኘበት መታሰር ሳይሆን ይረሸናል:: አንዱ አንዱን በሚከታተልበት የምድር እስር ቤት ውስጥ የዋህ ሆኖ መገኘት ሳይቀር ያስቀጣል::
ለማጠቃለል ያህል በእነዚህ የወያኔ እስር ቤቶች ውስጥ ስንት የታፈኑ የተገደሉ የሞቱ ኢትዮጵያውያን እንዳሉ ማሰብ የእያንዳንዱ ሰው ግዴታ ነው:: የወያኔው ጁንታ ማንም በማያውቀው ሁኔታ ለሃገር የሚያስቡ እና የሚጭነቁ ወገኖችን በጠላትነት በማየት በማፈን ደብዛቸውን የሚያጠፋባቸው እነዚህን ሰው በላ ምድር ቤቶች ማጋለጥ የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ግዴታ ነው::ሻሎም

Thursday, May 2, 2013

መድረክ ለመጠላለፍ መተነኳኮስ ጀምሯል!የወያኔ ታማኝ ጋዜጣ ሰንደቅ እያሟሟቀች ነው:;

 ምንሊክ ሳልሳዊ
በቅርቡ የአንድነት ፓርት መድረክን ገምግሜለሁ ያለበትን እና ወደ ዉህደት የሚለውን ጥናት የመድረክ አባላት አብጠልጥለውታል:: ዘላለማቸውን የፖለቲካ ግልቢያ በአደባባይ የሚያደርጉት ተቃዋሚዎች ዳግም ራሳቸውን ለመጣል በአደባባይ አንዱ የአንዱን ሃሳብ መዝለፍ ስራዬ ብለው ተያይዘውታል::
ይኸው ሁሌ ከኛ በላይ የለም የሚሉት የአዛውንቶች ክበብ የሆኑ ፓርቲዎጭ አንዱ አንዱን ለማዘዝ አምባገነንነትን ለማስፋፋት በሚል ዘይቤ ይመስላል አንዱ አንዱ ያንተ ስራ የመንገድ ላይ ስራ ነው በማለት መወራረፍ ጀምረዋል:: የአንድነት ብሔራዊ ም/ቤት መድረክ እንዲገመገም ማዘዝም ሆነ በዚህ ላይ ተመስርቶ የሚሰጠው ውሳኔ ተቀባይነት የለውም በማለት አንዱ አንዱን እያጣጣሉት ሲሆን በውስጥ ጉዳያቸውን መጨረስ ሲገባጨው በአደባባይ ለገዢው መደብ ታማኝ በሆኑ ጋዜትኦች ላይ እንዲህ መዘላበዱ የገዢውን ፓርቲ እድሜ ከማስረዘም ዉጪ ትግሉን ማክሰም ነው::
በበጎነት እና በትግል አጋርነት ስሜት የሚቀርቡ ሃሳቦችን በዉስጥ ተወያይቶ ተነጋግሮ መፍትሄ ማስቀመጥ ሲገባ በጠባብነት እና በብሄር ላይ ተመስርተው የተደራጁ ድርጅት መሪዎች የፖለቲካ ቋንቋ የተጠቀሙ እየመሰላቸው በይፋ እየዘለፉ የትግል ጓዶቻቸውን ማጥላላት ተገቢ አይደለም:; አንድነት ለመድረክ በጹሁፍ ባላቀረበው ጉዳይ ላይ መድረክን ማዘዝ አይችልም በሚል ፈጥኖ በአደባባይ አስተያየት መስጠት ሌላ ተእኮ ካልሆነ በስተቀር መድረክን እንደ ቅንጅት ለማድረግ የሚደረግ ሴራ ያስመስላል::
.....ዶ/ር መረራ ጉዲና.... ‘‘የመንገድ ላይ ስራ ነው’’ ሲሉ አጣጥለውታል። ሲል ሰንደቅ የተዘባበተበት መድረክ ነገ ምን ሊሆን ይችላል የሚለውን ካሁኑ መገመት አያቅትም::እርስ በርስ ተወነጃጅሎ መበታተን ነው እጣው??/ፖለቲካ እንሰራለን የሚሉ እንደዚህ አይነት ሰዎች ራሳቸው ፖለቲካዊ ጋር መጋባት ውስጥ እየዋዠቁ ሌላውን ግራ ተጋብቷል ማለት ያጠያይቃል::
የመድረክ የወቅቱ ሊቀመንበር አቶ ጥላሁን እንደሻው አንድነት ፓርቲ መድረክን የመገምገም ስልጣን የለውም ብለዋል። ያለው ወያኔያዊው ሰንደቅ የተቃዋሚ ፓርቲዎች መፈረካከስን የሚፈልግ መሆኑ በገሃድ ተደጋግሞ አይተነዋል ከዚህ ቀደም ኢንጂነር ዘለቀን ይዞ አላዘነ ዛሬ ደሞእነዚህን ...አቶ ጥላሁን የመድረክ ሊቀመንበር ናቸው እስከተባለ ድረስ አንዳንድ ጉዳዮችን በአደባባይ የማይነገሩ ዉስጥ ለውስጥ በንግግር የሚያልቁ የመድረክ አባል ፓርቲዎችን ጉዳይ በይፋ ስልጣን እንዳሌላቸው መናገር እብደት ይመስለኛል:: የአንድነት ብሔራዊ ምክርቤት ግምገማ ሙሉ በሙሉ ህገ-ወጥ ነው ማለታቸው ማንን ለማስደሰት ነው ወይስ እርስ በርሳቸው መባላት ጀመሩ ለማሰኘት???? አቶ ጥላሁን ?????
ዘላለማቸውን ከተኙበት የማይነሱት ተቃዋሚዎች አሁንም ለመጠላለፍ መነቋቆር መጀመራቸው በትግሉ ሂደት ዉስጥ እንቅፋት ለመፍጠር የሚራወጡበት ሁኔታ በስተርጅና እንኳን በፖለቲካ አለመብሰላቸውን ያሳያል:; በፖለቲካ ስድብ የበሰሉት እነዚህ የተቃዋሚ አመራሮች እርስበርሳቸው መጠላለፍን የሚያቆሙት መች እንደሆነ ይናፍቀናል::
እስከዚያ መልካሙን እንመኛለን::

አቶ ሃይለማርያም ለአውሮፓ ህብረት የገባውን ቃል አፈረሰ::የወያኔ የፖለቲካ ፍርድ ቤቱ በእነ እስክንድር ነጋ ላይ ፍርዱን አጸና::


አዲስ አበባ ያሉ ዲፕሎማቶች መታገስ ነው ይላሉ:;
ምንሊክ ሳልሳዊ

ባለፈው የአውሮፓን ህብረት ለመጎብኘት ወደ ብራስልስ ያመሩት አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ በህብረቱ በቆዩበት ጊዜ ተደጋግሞ ሲነሳላቸው የነበረው ጉዳይ የእስረኞች ጉዳይ እንደነበር ይታወቃል ::በዚህም መሰረት በሕወሓት መራሽነት የሚተሙት አቶ ሃይለማርያም እጅግ ጥብቅ የሆነ ቃል ገብተው ወደ ሃገር ቤት መመለሳቸውን የትላንት ዜናችን ነበር :; እንዲሁም ከዚህ ቀደም በተለያዩ ወቅቶች ሟቹ ጠ/ሚ የተለያዩ ገንዘቦችን እና መደለያዎችን ከህብረት በልማት ስም በመውሰድ ቃል እየገቡ ነገሩ ጎትተውት አልፈዋል:: ህብረቱ የልማት እርዳት ሲያደርግ የነበረ በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ያለውን የተካረረ ነገር ላማላልት እና ወደ ስብኣዊ መብቶች ላይ ለማተኮር መሆኑን በተደጋጋሚ ገልጿል::

ከወደ አዲስ አበባ ዛሬ በፍርድ ቤቱ አሳዛኝ ፖለቲካዊ ውሳኔን ተከትሎ በሃገር ውስጥ ያሉ የተለያዩ ዲፕሎማቶች ሁኔታው ከማስገረምም አልፎ አስደንግጦናል ሲሉ ተደምተዋል:: ሆኖም የመንግስታቹህን ጭራ ለመያዝ ይከብዳል የሚሉ ዲፕሎማቶች ነገሮችን በትእግስት መመልከት እና መጠበቅ ነው ሁኔታዎች ሊቀየሩ ይችላሉ የውስጥ አጣብቂኞች የፈጠሩት ውሳኔ ይሆናል ምናልባት......የጀመርነውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እንቀጥላልን ብለዋል::

ዛሬ በጠቅላይ ፍርድቤት የዋለው የፍርድ ሂደት በእስንድር ነጋ የ18 አመት እና አንዷለም ላይ የእድሜልክ እስራት ያጸና ሲሆን ዳኛው የወያኔ ጀሌው ዻኜ መላኩ ክሱም ሆነ ውሳኔው ትክክል እና ምንም አስተያየት ሊደረግለት የማይችል ሲል ከታሪክ ተጠያቂነት የማይድንበትን አስተያየት የሰጠ ሲሆን ሌሎች የጠቅላይ ፍ/ቤ ዳኞች አናየውም ብለው እስከ በላይ አካል ክርክር የተኬደበትን ጉዳይ ከምን ሞራል እንዲህ ሊደመድምበት እንደቻል ጊዜ ይጠይቀዋል::
እንደዚህ አይነት በፍትህ ላይ ጠባብ አመለካከታቸውን እና ጸረ ህዝብ አቋማቸውን የሚያራምዱ ዳኞችን መከታተል እና ከየተደበቁበት ጊዜ ጠብቆ መጋለጥ የዜግነት ግዴታ ነው:: ይህ መንግስት ሲወድቅ በተለያዩ የአውሮፓ እና የአሜሪካ ከተሞች ለመመሸግ እያለሙ የሚገኙት የፍትህ አካላትን መከታተል ግዴታችን ነው::

ከፍርዱ በኋላ "እውነት ነጻ ታወጣናለች!!!" ያለው እስክንድር ነጋ "የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ እውነት በራሱ ጊዜ እንደሚወጣ ለኢትዮጵያውያን ማሳወቅ እንፈልጋለን "ብሏል:የተከሰሱበት ጉዳይ በአሸባሪነት እና አሸባሪ ተብሎ በተፈረጀው ከግንቦት ሰባት ጋር ግንኙነት አላቹህ ተብለው ቢሆንም ከዚህ በፊት ጉዳዩን እንዲያዩት ይግባኙ የቀረበላቸው ዳጛ አማረ አሞኘ ይህን ክስ ለማየት የሚያስችል በቂ ማስረጃ ስላሌለ በነጻ እለቃቸዋለሁ በማለታቸው ጉዳዩ ከሳቸው እጅ ተነጥቆ ፖለቲካዊ ዉሳኔ እንዲሰጥበት ተደርጓል::
በኢትዮጵያ እየተፈጸመ ያለው የፍርድ ቤት ስርኣት እና ውሳኔዎች በአለም አቀፍ ደረጃ አነጋጋሪ ከሆነ ረዥም አመታትን ያስቆጠረ ሲሆን የወያኔ ካንጋሮ ፍርድቤት እና ያልሰለጠኑ በፖለቲካ ታማኝነት ዳኛ የሆኑ ያልበሰሉ ካድሬዎች እየወሰዱ ያለው ህገወጥ እርምጃ እና ውሳኔ ነገ እንደማያስጠይቃቸው ሆነው መታየታቸው ሃገር ምን ያህል በፍትህ እጦት ቀውስ ውስጥ እንደሆነች ያሳያል:; ለግል የወያኔ ጥቅማጥቅሞች እና የኑሮ ምጮት እየተገዙ ያሉት የህግን ከለላ እንኳን ምን ያህል ስሜቶችን መረዳት ያልቻሉ ፍርደገምድል ዳኞችን መፋረድ ግዴታችን ነው::
እስክንድር ነጋም ሆኑ ሌሎች እስረኞች ቀን ሳይረዝም በቅርብ ጊዜ እንደሚለቀቁ ባለሙሉ ተስፋ ስሆን ይህ ደሞ ወያኔ እየደረሰ ያለበትን ኪሳራ እያሳየን ነው :: በተለያዩ የአውሮፓ እና የሰሜን አሜሪካ ከተሞች ወያኔ እየደረሰበት ያለውን ውርደት ለማካካስ እየተጠቀመበት ያለው ስልት እንደማያዋጣው ልንነግረው ይገባል::
ዲያስፖራው ትግሉን ያቆማል ብሎ የሚያስብ ከሆነ ዘላለሙን በጫካ ሞኝነት ራሱን የሚነዳው ወያኔ ልክ እያስገባነው መሆኑን አልተረዳውም:; በተከታይነት ደሞ በቀሪ የህሊና እስረኞች ላይ ሊወስን የተዘጋጀውን እየጠበቅን ትግሉ ግን ወያኔ አፈር እስኪገባ እንደሚቀጥል ለመናገር እወዳለሁ :: ትግሉ ይቀጥላል!!!